የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ እና የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን የኒውክሊየር ኃይል ማመንጫ የሚውሉ አመቺ የሆኑ የቦታ መረጣ ጥናት ለማድረግ የአማካሪ ውል ስምምነት ተፈራረሙ

የአማካሪ ውል ስምምነቱን የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ሥራ አስፈጻሚ ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ተከተል ዮሐንስ እና የኢትዮጵያ የኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሳንዶካን ደበበ ተፈራርመዋል።

ስምምነቱ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሰላማዊ ተግባር የምትገነባውን የኒውክሊየር ኃይል ማመንጫ ቦታ በጥናት ለመለየት የሚያስችል ሲሆን ጥናቱም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያላቸው መስፈርቶችን የተከተለ፣ ደህንነቱ አስተማማኝ እና ተስማሚ የሆኑ ቦታዎችን ለመለየት ይረዳል።